Friday, November 26, 2010

የእግዚአብሔር መልስ(2)

                         የእግዚአብሔር መልስ፡-(2)          
                   ልጄ ሆይ!
•ጌታን ስትጠብቀው ቢዘገይብህ እንዲህ በል…
* * *
“በእግርጥ ጌታ ይመጣል …መቼ እንደሚመጣ ግን አላውቅም። ከእኔ የሚጠበቀው የሚመጣበትን  ቀን ማወቅ ሳይሆን እንደሚመጣ ማመን ነው።”
* * *
•በመከራና በፈተና ውስጥ ስትሆን ደስታ እንዳይርቅህ እንዲህ በል…
                         * * *
“መከራና ፈተና በአማኝ ውስጥ ደስታን እንጂ ጭንቀትን አይፈጥሩም!!”
                         * * *
•ተስፋ እንዳትቆርጥ ይህን መዝሙር ከዳዊት ጋር ዘምር…
                         * * *
“እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ ልብህም ይጽና እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ” መዝ.26፡14
·        ችግር ሲገጥምህ እንዲህ በል…
                   * * *
“እኔ ባላውቅም ከዚህ ችግር በስተጀርባ አንድ በጎ ነገር አለ…ማንኛውም አይነት መጥፎ ነገር ቢኖርም እንኳን አንተ ቸር እና ሰውን የምትወድ አምላክ ስለሆንክ ለበጎ አድርገህ ትቀይረዋለህ”
                     * * *
·        ሰይጣን በኃጢአትህ ተስፋ እንዳያስቆርጥህ በልብህ እንዲህ በል…
“በሰዎች ዘንድ ያለው ኃጢአት ሁሉ ከእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት ጋር ሲነጻጸር በውቅያኖስ ውስጥ እንደተጣለ ፍንጣቂ ጭቃ ይቆጠራል”
·        ለጸሎት በቆምክ ጊዜ ማለት ስላለብህ ነገር ብዙ አትጨነቅ…
                           * * *
“እግዚአብሔር አምላክ ገና ፊቱ ስትቆም ቃላቶችህን ከመናገርህ በፊት ምን ማለት እንደፈለግህ የልብህን ያውቃልና፤ ሳትለምነው ምን እንደምትሻ ያውቃልና…”
                           (አምላክህ አልፋና ዖሜጋ እግዚአብሔር)

የእግዚአብሔር መልስ(1)

የእግዚአብሔር መልስ፡-(1)
                          ልጄ ሆይ!
ላመንክብኝ እምነትህ በይቅርታዬና በፍቅሬ ላይ ጣለው። ብዙ ጊዜ ከአንተ የራቅሁ ይመስልሃል፤ነገር ግን ምን ጊዜም ከአጠገብህ አልለይም፡ በጣም ቅርብህ ነኝ። ሁሉ ነገር ያልተሳካልህ መስሎ የሚታይህ ጊዜም እንዳለ አውቃለሁ፤ ነገር ግን ልጄ ሆይ ምን ያህል እንደምታምንብኝ ትለካበታለህ እንጂ አትጠፋበትም።

ሁኔታዎች አንተ እንዳሰብካቸው እና እንዳቀድካቸው ባይሰምሩልህ ወይም ሳይሳኩልህ ቢቀሩ፤ ወድቀሃል ማለት አይደለም። እንዲያውም ሁኔታዎችን አዝነህና ተክዘህ ልትመዝናቸው አይገባም። ይልቁንም የወደፊቱ ህይወትህ ድቅድቅ ጨለማ የዋጠው መስሎ በሚታይህ ወቅት እንኳን ተስፋ መቁረጥን ከልብህ አውጥተህ ጣለው፤ ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አስወግዶ ይጥላልና።

ያንተ ድርሻ የተቻለህን ማድረግ ብቻ ነው፤ የቀረውን ለእኔ ተወው።

እኔ የፈጠርኩህ እና እጅግ አድርጌ የማፈቅርህ አምላክህ ነኝ። የልብህ ሃሳብና ምኞት ቁልጭ ብሎ ይታየኛል።

ዘለዓለማዊው ደኅንነትህ ትልቁ ፈቃዴ ነው፤ ስለሆነም በዕለት ህይወትህ የተዘበራረቀ ሁኔታ ቢገጥምህም እንኳን በበጎ እለውጠዋለሁ።

ምንም ነገር ከአንተ ብወስድ ጎደለብኝ ብለህ አታጉረምርም፤ የእኔ የምትለው አንዳች ነገር የለምና። እንኳን የአንተ የሆነው ነገር አንተም የእኔ ነህ፤ ሁሉም የእኔ ነው። ካለ እኔ ምንም ነህ፤ ሌላው ቀርቶ ጠንካራው ችግርና መከራ ተከትሎ የሚያመጣውን በረከቴን አስብ።

ይህም ብቻ አይደለም፤ ማብቂያ የሌለው ለአንተ ያለኝን ፍቅር እና በህይወት ዘመን ሁሉ የምትመራበትን ጥበብ እንደምታገኝ አትዘንጋ።

በህይወትህ በእኔ ፈቃድ ያለፈ ሁሉ አንተ አንተን ከምትወደው በላይ ስለምወድህ የሆነ መሆኑን አውቀህ ተቀበለው።

ስለሆነም በምንም ሁኔታ ውስጥ አታጉረምርም። ከሁሉም በላይ የሆነ ፀጋዬ ይጠብቅሃል፤ በርታና በሠላም ተቀበለው ውጤቱም ደስታና በረከት ሆኖ ታገኘዋለህ።

                              (አምላክህ አልፋና ዖሜጋ እግዚአብሔር)

Saturday, November 20, 2010

God's answer to our prayer.

www.tewahedo.se
የእግዚአብሔር መልስ፡-
ሌጄ ሆይ!

በብዙ ሀሳብ እና ጭንቀት፤እንቅልፍም በማጣት ቀናትን እንዳሳለፍክ አያለሁ።

ሰው ራሱን ከሚጎዳው በላይ  አንዳች የሚጎዳው ነገር የለምና ለዚህ ሁሉ ችግር ተጠያቂው አንተ እንጅ እኔ አይደለሁም። ነገር ግን እኔ አባትህ ከምትችለው በላይ ትፈተን ዘንድ አልፈቅድምና ችግሮችህን ሁሉ በሠላም ታልፋቸዋለህ።

ምን ጊዜም ቢሆን በፍርሃትና በጭንቀት እንዳትወድቅ እኔ ለአንተ የገባሁልህ ቃል ኪዳንና የማደርግሌህን ጥበቃ አትርሳ። ችግር በገጠመህ ጊዜ ሁለ እኔ አባትህ እንደምጠብቅህና እንደምንከባከብህ አስታው። ለነፍስህ እረፍት እንድታገኝ በጭንቀትህ ሰዓት እኔ የተናገርኳቸው ቃላት ፊት ለፊት አስቀምጣቸው… “በህይወትህ ዕድሜ ሁለ ማንም አይቋቋምህም፤  አልጥልህም…አልተውህም” ኢያ.1፡5 “እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፤ ማንም ክፉ ሉያደርግብህ የሚነሳ የለምና አትፍራ” ሐዋ.18፡10
ሌጄ ሆይ!

የሚፈራና የሚጨነቅ ሰው የእኔን ፍቅና ቃል  ኪዳን የረሳ ሰው  ስለ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ይልቁን በአንተ ላይ  የሚደረገው ነገር ሁለ ከእኔ ፈቃድ ውጭ እንልሆነ ልትገነዘብ ያስፈልጋል። እንኳን  ሌላ የራስ ፀጉርህም በእኔ ዘንድ የተቆጠረ ነው።
ይህ ሁለ የተስፋ ቃሌ በፈተና ጊዜ ከሚመጣ ከጥርጥር ውጊያ ሊታደግህ ይችላል። ስለዚህ እኔ ለአንተ በምሰራልህ ሥራ ላይ መተማመን፤ተስፋንና ጥልቅ እምነትን የሚያረጋግጡ ጥቅሶችን በልብህ አጥናቸው፤በህሊናህ ውስጥ አስቀምጣቸው፤እንዳትረሳቸው መልሰህ ድገማቸው
ሁሌ ጊዜ በእኔ ደስ  ይበልህ፤ በአንተ ውስጥ ያለችውን ነፍስ በአርአያና በአምሳሌ የፈጠርኳት እኔ  ስለሆንኩ ከእኔ በስተቀር ይህችን ነፍስ ማንም ሊያስደስታት አይችልም። ከእኔ ተለይተህ በመኖር ደስታን አገኛለሁ  ብለህ ፈጽሞ አታስብ።
ምንም ነገር ቢሆን ሁለም ለበጎ ነውና እኔ ከአንተ ጋር እስከሆንኩ ድረስ በአንዳች አትከፋ። በጭንቀትህ ወቅትም አብሬህ እንደምጨነቅ ልብ በል።

የተስፋን ቃል የሰጠሁህ እኔ አባትህ ታማኝ ነኝና ባለህበት ቦታ ሆነህ በፍቅር ጠብቀኝ።ጆሮዬን ወደ አንተ ዘንበል አድርጌ ጩኸትህን እሰማለሁ፤ እንባህንም ከዓይንህ ላይ አብሳለሁ፤ አንተም በሁለት እግርህ ቆመህ ማዳኔን በሰው ሁሉ ፊት ትመሰክራለህ።

Saint Michael songs

Saint Michael songs

My Lord when are you coming?

My Lord why You love me this much?